Overview News

የአረጋውያን ቀን አከባበር

2 January 2024 Aswin Endeman

በቅርቡ በባቱ/ዝዋይ ተከበረውን የአረጋውያን ቀንን ስፖንሰር በማድረግ በማህበረሰባችን ውስጥ ያሉ አረጋውያን ያበረከቱትን አስተዋጾ ለማክበር እና ለመዘከር እንዲሁም ለማድነቅ የተዘጋጀ ድንቅ ቀን ነበር። ዝግጅቱ የአረጋውያን   ጠቃሚ ሚና በመገንዘብ ልምዳቸውን ለተተኪው ትውልድ የሚያካፍሉበት መድረክ እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመም ነበር።

ክቡር አቶ አህመዲን እስማኤል (የከተማው ከንቲባ) ካደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በፊትም ከዚህ አለም በሞት የተለዩትን የአረጋውያን በማስታወስ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎትም እንዲደረግ አስተባብረው ነበር።

ሼር ኢትዮጵያም ከ500 ኪሎ ግራም በላይ የበቆሎ ዱቄት እና 50 ሊትር የምግብ ዘይት ለ50 አረጋውያን በስጦታ መልክ  በማስረከብ ለዝግጅቱ ያለውን ተሳተፎም በቀናነት አሳይቷል።