Overview News

በሼር ኢትዮጵያ እስታዲየም ሲካሄድ የነበረው ጨዋታ ተጠናቀቀ

31 May 2023 Aswin Endeman
በሼር ኢትዮጵያ እስታዲየም ሲካሄድ የነበረው ጨዋታ ተጠናቀቀ

በኢትዮጵያ የግር ኳስ ፌደሬሽን አመራርነት ከተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ተዉጣጥተው በምድብ C  ተከፍለዉ ወደ ሼር ኢትዮጵያ እስታዲየም ተልከዉ የነበሩ 13 ቡድኖች ለተከታታይ ሁለት ወራት ሲያካሂዱ የነበረዉን የስልጠና እና የጨዋታ መርሃግብር  ያለምንም  የእስታዲየም ወጪ አጠናቀው ባሳለፍነው ሳምንት ወደ መጡበት ተመልሰዋል፡፡

በፍፃሜው ጨዋታም የካ ክፍለ ከተማ ከአዲስ አበባ እና ሀበሪቾ ከደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን ተጋጥመው  ሀበሪቾ 1-0 አሸንፏል። አሸናፊዎቹን እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በስታዲየማችን በርካታ ተመልካቾች እና ደጋፊዎቻቸው ብዙ አጓጊ ጨዋታዎችን በመመልከት  በመቻላቸው ደስተኞች ነን።

ሼር ኢትዮጵያ ለመረሃግብሩ መሳካት ሲያበረክት ለነበረዉ አስተዋፅኦ በፌደሬሽኑ እና በስፖርት ማህበረሰቡ ግንዛቤ ውስጥ በመግባቱና ይህንንም ማረጋገጥ ያስቸል ዘንድ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል፡፡