Overview News

የመንገድ ደህንነትን ለማሻሻል የፍጥነት መገደቢያዎች ከዝዋይ እስከ አዳሜ ቱሉ ባለው መንገድ ላይ ተቀመጡ

3 May 2024 Mariska Braam

በኢትዮጵያ,  እርሻዎቻችን  በሙሉ ከአዲስ አበባ ሞያሌ በሚያገናኘው ዋና መንገድ ተጓዳኝ ላይ ይገኛሉ። ይሁንና አዲስ የተሰራውም የፍጥነት መንገድ የመንገደ ትራፊክ መጨናነቅን ቢቀንስም፣ በሚያሳዝን ሁኔታ አሁንም ብዙ የትራፊክ አደጋዎች በመንገዶቹ ላይ ይስተዋላሉ  ስለዚህም  ፍጥነትን የሚቀንሱ የመንገድ ላይ ጉብታዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ላለፉት ጊዜያቶች ስንታትር የነበረው በዚህም የተነሳ ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በቦታው በመገኘት በእርሻዎቻችን አካባቢ በአጠቃላይ 6 የፍጥነት  መገደቢያ ጉብታዎችን አስቀምጦ የነበረው ለትብብሩም የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ከልብ ለማመስገን እንወዳለን። በመጨረሻም ለሰራተኞቻችን እና ለማህበረሰቡ የተሻለ አገልግሎት   እንደሚያስገኙ ተስፋ እናደርጋለን።