Overview News

የአለም አቀፍ የሴቶች ቀን አከባበር በሩዋንዳ

4 April 2023 Aswin Endeman
የአለም አቀፍ የሴቶች ቀን አከባበር በሩዋንዳ

ከመጋቢት 12__15 / 2015 በፌርትሬድ የተመዘገቡ እርሻዎች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በዱኩንዴ ካዋ ሙሳሳ የቡና እርሻ በኪጋሊ ሩዋንዳ አንድ ላይ አክብረዋል። ተሳታፊዎቹ ከኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ኮንጎ፣ ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያ የተውጣጡ ነበሩ። ሼር ኤትዮጵያን በመወከልም ወ/ት ሕሊና ደበበ መኮንን የመረሃ ግብሩ ተሳታፊ ነበረች ።

ቡድኑ እንደ ዱኩንዴ ካዋ ሙሳሳ ኪጋሊ አቅራቢያ የሚገኘውን የቡና እርሻ የመሳሰሉ በርካታ ኩባኛዎችን ጎብኝቷል። እ.ኢ.አ በ2003  የተመሰረተው ይህ ኮፕሬቲፍ ከ300 ቡና አብቃይ ገበሬዎች ወደ 2,000 በላይ አድጓል። ሰማንያ በመቶው የዱኩንዴ ካዋ አባላት ሴቶች ሲሆኑ። ቡናቸውንም ”በሴቶች የመረተ ቡና ” ብለው ለገበያ ያቀርባሉ። ፌርትራድ ፕሪሚየም በመጠቀም ለህፃናት ትምህርት እና ማህበረሰቡን በቀጥታ የሚደግፉ ፕሮጀክቶችን ለምሳሌ እንደ ልብስ ስፌት ያሉ ለአካባቢው ገበያ እንደገና ጥቅም ላይ የሚውሉ የንፅህና መጠበቂያ ፓድዎችን የሚያመርት ነው። በካጄራ የህብረት ስራ ዩኒየን ሴቶችና ወጣቶች በሳሙና አመራረት እና በንብ ማነብ ላይ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።

በእርሻችን እና በማህበረሰባችን ውስጥ የሴቶችን ሚና እና አቋም ማስከበር ለተለያዩ እና አካታች የሰው ሃይል በምናደርገው ጥረት ወሳኝ ግብ ነው። ለሰራተኞቻችን እና ለእዚህ አላማ አስተዋፅኦ ለሚያደርጉ የማህበረሰብ አባላት የተለያዩ ፕሮግራሞችን እና የስልጠና ኮርሶችን መስጠቱን እንቀጥላለን፣ በአለምአቀፍ ሁኔታ ከሌሎች እርሻዎች ለመማር እድል ስለሰጠን ፌርትሬድን ልናመሰግነው እንፈልጋለን በማለት ፕሮግራማቸውን አጠናቀዋል።