Overview News

350 ሴት ልጆች እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ መላ ለእርሷ የተሰኘ የንፅህና መጠበቂያ ፓድዎች ተለግሰዋል

12 January 2024 Aswin Endeman

በ2015 መኸር ላይ የተጀመረውን ፕሮጀክት ተከትሎ፣ በቅርቡ በሼር ትምህርት ቤቶቻችን እድሜያቸው ከ12 እስከ 13 ዓመት የሆናቸው 350 ሴት ልጆች እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ የንፅህና መጠበቂያ ፓድዎችን ሰጥተናል. ይህ ሊሆን የቻለው በኔዘርላንድ የአበባ ፋውንዴሽን ከፍተኛ ድጋፍ ነው።

መላ በአማርኛ መፍትሄ ማለት ሲሆን የሚያመለክተውም በሚያሳዝን ሁኔታ በአፍሪካ ውስጥ ለብዙ ወጣት ሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ ላለው ችግር መፍትሄ ማበጀት ሲሆን ይህም ተመጣጣኝ የሆነ የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች እጥረትን ለማቃለል ያሰበ ሲሆን በአፍሪካ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ያሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ልጃገረዶች ለትምህርት፣ ለጤና፣ በራስ  ካለመተማመን በላይ ለሰብአዊ መብቶች እንቅፋት ይፈጥራል ብሎም ለብዙዎች የወር አበባ መጀመር ማለት በትምህርት ቤት ውስጥ ቀሪ እንዲበዛም ያደርጋል።

መላ እርሷ ሴቶችን እና ልጃገረዶችን በመላው ኢትዮጵያ በተመጣጣኝ ዋጋ እና ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የወር አበባ ምርቶችን እና የወር አበባን የጤና ትምህርት በመስጠት ህይወትን የሚቀይር የኢትዮጵያ ማህበራዊ ጀማሪ ድርጅት ነው.

በዚህ ፕሮጀክት፣ ሼር-ትምህርት ቤቶች፣ መላ ለእርሷ እና የደች አበባ ፋውንዴሽን ተባብረዋል. የባለሙያዎች ቡድኑ ፓድ ከመስጠቱ በተጨማሪ የሼር ትምህርት ቤት መምህራንን በማሰልጠን በልጃገረዶች ክበብ በኩል ሁሉም ልጃገረዶች በወር አበባ ጤና ላይ ስልጠና ይሰጣቸዋል.

መላ እርሷ ለቡድኑ ፍሬያማ ትብብር ማመስገን እንፈልጋለን እንዲሁም የደች አበባ ፋውንዴሽን ላደረጉት የማይናወጥ ድጋፍ ከልብ እናመሰግናለን. ልጃገረዶች በህይወት ውስጥ ያላቸውን ሙሉ አቅም እንዲደርሱ በማስቻል የክብር መብታቸውን የሚደሰቱበት ዓለም በጋራ እናበረክታለን።