Overview News

የማሕፀን ጫፍ ካንሰር ምርመራ

22 July 2022 Aswin Endeman

ሼር ኢትዮጵያ ሆስፒታል ግራውንድስ ፎር ሄልዝ (Grounds for Health) ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር ዕድሜያቸው ከ 30-50  ውስጥ ለሚገኙ ሴት ሠራተኞቻችን ነጻ የማሕፀን ጫፍ ምርመራ ለማድረግ የሚያስችል ዘመቻ አስጀምረናል። የዘመቻዉም ዓላማ ሴት ሠራተኞች በመሀፀን ካንሰር በሽታ እንዳያዙ ለመከላከልና በሽታውን በሕክምና መዳን በሚችልበት ደረጃ ላይ እያለ መኖሩ ከታወቀ በኃላ አስፈላጊውን ሕክምና መጀመር እንዲቻል ማድረግ ነው። ምርመራው የማሕፀን ሕዋሳትን ጤና እንዲዛባ የሚያደርገውን ሂዩማን ፓፒሎማ ቫይረስ / ኤችፒቪ/ (human papilloma virus /HPV ) የሚባለውን አደገኛ ቫይረስ መኖር እና አለመኖሩን ያጣራል። አብዛኛዎቹ የማሕፀን ካንሰር ዓይነቶች ከአደገኛው ኤችፒቪ ቫይረስ ጋ ግንኙነት አላቸው።

የግራውንድስ ፎር ሄልዝ ሐኪም የሆኑት ዶ/ር ደምስ እንደሚሉት በሠራተኞች መካከል ስለ በሽታው ግንዛቤ እንዲኖር ማድረጉ በጣም አስፈላጊ ነው። እሳቸው ከሕክምና ቡድናቸው ጋ አንድ ላይ በመሆን በነፍስ ወከፍ ምርመራ ከመደረጉ በፊት በአነስተኛ ቡድኖች ለተደራጁ ሠራተኞች የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ። ድንገት ሠራተኛዋ ውጤቷ ፖዘቲቭ ሆኖ ቢገኝ፣ ሕክምናው ይሰጣታል። የግራውንድስ ፎር ሄልዝ ሥር የሚሠሩትን እነዚህን አጋሮቻችንን ለሚያደርጉልን ድጋፍ በሙሉ እያመሰገንን ሁሉም ሴቶቻችን ተሳታፊ እንዲሆኑ ከወዲሁ እንጋብዛለን።