Overview News

በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎድ ማህበረሰቦች የሚውል የምግብ እርዳታ

14 April 2023 Aswin Endeman

ባለፈው አመት በቦረና ዞን ድርቅ ተከስቶ ለሰብል ውድመት እና ለከብቶች ሞት ምክንያት ሆኗል ። ይህም በዘንድሮው አመትም በድጋሚ በመከሰቱ  ህዝቡን ለመደገፍ ሀገር አቀፍ ዘመቻ ተጀምሯል። ሼር ኢትዮጵያም ዘመቻውን በመቀላቀል  13 ቶን የበቆሎ ዱቄት ገዝቶ ፣ አርብ  መጋቢት 29  ለባቱ/ዝዋይ  ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት   እና የተወሰኑ ሌሎች አመራሮች  በተገኙበት ርክክብ ተፈጽሟል ። እነሱም የተረክቡትነ የምግብ እህል በወቅቱ ለተጠቃሚዎች እንደሚያደርሱ ቃል ገብተዋል።