Overview News

አፍሪፍሎራ ሼር ፣ ቫን ዲጅክ ፍሎራ እና የኔዘርላንድ ፍላወር ፋውንዴሽን በጋራ በመሆን ለሼር ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ወተት /እርጓ /የመመገብ ፕሮጀክትን አስጀመሩ።

26 October 2022 Aswin Endeman
በሼር ኢትዮጵያ ት/ቤት የወተት ፕሮግራም ተሳታፊ ተማሪዎች

ፕሮጀክቱም በዚህ የትምህርት ዘመን እድሜያቸዉ ከ4 እስከ 6 ዓመት የሚሆናቸው 1350 የሚሆኑ የሼር ኢትዮጲያ ትምህርት ቤቶች  ተማሪዎች በሳምንት ሁለት ጊዜ በጤናማ ንጥረ ነገሮች የበለጸገ የፕሮቲን እርጎ እንዲያገኙ ይረዳል። በአንድ ጊዜ የወተት ምገባ ለ አንድ የ5 አመት ልጅ ዕለታዊ የፕሮቲን ፍላጎት 33% እና 10% የቀን ካሎሪ ይሰጠዋል. እርጎው በየእለቱ ሁሉም ልጆች በትምህርት ቤት በሚያገኙት ትኩስ ምግብ ጋር አብሮ ይሰጣል ።

በፕሮጀክቱም ድጋፍ ልጆቹ የሚያስፈልጋቸውን የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ ያግዛል። በዚህ መንገድ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ስጋትን በመቀነስ የህጻናትን ትምህርት ተሳትፎ እንጨምር እናደርጋለን። ይህም ፕሮጀክት ከአስራ ስድስት ላላነሱ ሰዎች የሥራ እድል የሚሰጥ ሲሆን እንዲሁም ከሁለት በባቱ/ ዝዋይ / ውስጥ ከሚገኙ የወተት ተዋጽኦ አምራችና አቅራቢ ድርጅቶች ጋር የስራ ዉል ተፈራርመናል።

ከአጋሮቻችን ቫን ዲጅክ ፍሎራ እና የኔዘርላንድ ፍላወር ፋውንዴሽን ላደረጉልን ለዚህ ለጋስ እርዳታ በሁሉም የሼር ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች፣ ወላጆች እና አስተማሪዎች ስም እጅጉን የላቀ ምስጋና ልናቀርብላቸዉ እንወዳለን።

በሼር ኢትዮጵያ ት/ቤት የወተት ፕሮግራም ተሳታፊ ተማሪዎች በሼር ኢትዮጵያ ት/ቤት የወተት ፕሮግራም ተጠቃሚ ህፃን በሼር ኢትዮጵያ ት/ቤት የወተት ፕሮግራም ተሳታፊዎች በሼር ኢትዮጵያ የወተት ፕሮግራם ተጠቃሚ ተማሪዎች በሼር ኢትዮጵያ ት/ቤት ተማሪዎች የወተት ፕሮግራም ላይ በሼር ኢትዮጵያ ት/ቤት የወተት ስርጭት ሥነ-ሥርዓት በሼር ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ውስጥ ተማሪዎች ወተት እየተመገቡ Sheer fi Vaan diik Floraa garee hojii waliin mari'achaa jiru Sheer fi Vaan diik Floraa sagantaa leenjii gaggeessaa jiru Sheer fi Vaan diik Floraa barattoota waliin mari'achaa jiru Sheer fi Vaan diik Floraa bakka pirojeektii aananii mana baruumsaa keessatti hojjetaa jiru