Overview News

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጉብኝት

24 May 2023 Aswin Endeman
Hawassa University students visiting

ቅዳሜ ግንቦት 12 /2015 ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተጋበዙ የሆርቲካልቸር እና የዕፅዋት ሳይንስ ተማሪዎችን እንዲሁም መምህራንን አስተናግደናል። አቀባበል ከተደረገላቸዉም በኋላ ስለ እርሻዉ እንቅስቃሴ አጭር መግቢያ ተሰጥቷል በዚህም ላይ የኩባንያው CSR ተግባራትም ተብራርተዋል. በመቀጠልም የግሪን ሃውስ፣ የደረጃ አሰጣጥ፣ የዌት ላንድ እና  የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል።

ኩባንያው አካባቢያዊ እና ማህበራዊ መስተጋብሩን ተግባራዊ በሆነ መልኩ ለማሳየት ጥሩ አጋጣሚ የፈጠረለት ነበር፡፡. በመጨረሻም ተሳታፊዎቹ ሼር ኢትዮጵያ በማህበራዊ አገልግሎትና በአካባቢ ጥበቃ ላይ እያስመዘገበ ያለው ልማት እንዳስደነቃቸው ገልፀዋል።

እነዚህ ተማሪዎች በኢትዮጵያ በአበባ፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ ብሩህ ተስፋን ለመገንባት ትልቅ ሚና እንደሚጫወቱ ተስፋ እያደረግን ይህንን ዝግጅት በማቀዱና በማዘጋጀቱ EHPEAን እናመሰግናለን።