Overview News

የደን ልማትና ክብካቤን ለማሳደግ የተደረገ የ57.000 ችግኝ ተከላ መርሃግብር

22 July 2022 Aswin Endeman

በዓመታዊው የኢትዮጵያ የ 2014 ዓ.ም. የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ፣ የችግኝ ተከላ ወቅት፣ ሐምሌ 11 ቀን በዝዋይ/ ባቱ ዎርጃ ተራራ ላይ እና በቆቃ በርካታ ችግኞች /በቁጥር 57.000 ተክለናል። በዚህም ምክንያት ከ 2009 ጀምሮ የተከልናቸውን ችግኞች ብዛት ወደ 1 ሚሊዮን እንዲጠጋ ለማድረግ ችለናል። ዘላቂነት ያለው የደን ጥበቃ ማድረግን እና የርጃ ተፋሰስን በብልሃት ተጠቃሚ መሆን መቻልን ማረጋገጥ ዋንኛ ዓላማው በሆነው በዚህ ፕሮጄክት ሥር፣ ሼር፣ አይዲኤች እና ቪክዳ የደን መራቆትን እና የአየር ንብረት መዛባትን በሚከተሉት ጥረቶች ለመዋጋት አንድ ላይ በትብብር በመሥራት ላይ ይገኛሉ፦

  • የደን ልማትና ክብካቤ እና ኤኮ-ቱሪዝምን ማልማት (በግምት 285 ሄክታር የወል መሬት)
  • የተጎዱ አካባቢዎች ላይ ትናንሽ ሸለቆዎችን በመቆፈርና የአፈር መሸርሸርን መከላከያ የግንብ አጥሮችን በመሥራት እንዲያገግሙ ማድረግ
  • የሚታጨድ ሣር ዘርን መዝራትና የከብት መኖ አጠቃቀምን ማሻሻል
  • ገቢ ማስገኛ እንቅስቃሴ የሚያከናውኑ ቡድኖችን ማቀናጀት (ለአብነት ንብ ማነብ ሥራ)
  • ጥሩ የእርሻ ዘዴዎችን ማስተማርና ተፈጻሚ ማድረግ፣ ለምሳሌ የአካባቢው አርሶ አደሮች ምርጥ ዘር እንዲጠቀሙ ማድረግ

የመጨረሻው ግብ ፕሮጄክቱ በማኅበረሰቡ በራሱ እንዲታዳደርና ጥበቃ የተደረገለትን አካባቢ በባለቤትነት እንዲይዝ ማድረግ ነው።

9 የተለያዩ አገር በቀል የዛፍ ዓይነቶችን እንድንተክል ላገዙን ለሠራተኞቻችን እና ለሁሉም በጎ ፈቃድ ተሳታፊዎች በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን።