Overview News

አፍሪፍሎራ ሼር ፣ ቫን ዲጅክ ፍሎራ እና የኔዘርላንድ ፍላወር ፋውንዴሽን በጋራ በመሆን ለሼር ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ወተት /እርጓ /የመመገብ ፕሮጀክትን አስጀመሩ።

26 October 2022 Aswin Endeman
አፍሪፍሎራ ሼር ፣ ቫን ዲጅክ ፍሎራ እና የኔዘርላንድ ፍላወር ፋውንዴሽን በጋራ በመሆን ለሼር ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ወተት /እርጓ /የመመገብ ፕሮጀክትን አስጀመሩ።

ፕሮጀክቱም በዚህ የትምህርት ዘመን እድሜያቸዉ ከ4 እስከ 6 ዓመት የሚሆናቸው 1350 የሚሆኑ የሼር ኢትዮጲያ ትምህርት ቤቶች  ተማሪዎች በሳምንት ሁለት ጊዜ በጤናማ ንጥረ ነገሮች የበለጸገ የፕሮቲን እርጎ እንዲያገኙ ይረዳል። በአንድ ጊዜ የወተት ምገባ ለ አንድ የ5 አመት ልጅ ዕለታዊ የፕሮቲን ፍላጎት 33% እና 10% የቀን ካሎሪ ይሰጠዋል. እርጎው በየእለቱ ሁሉም ልጆች በትምህርት ቤት በሚያገኙት ትኩስ ምግብ ጋር አብሮ ይሰጣል ።

በፕሮጀክቱም ድጋፍ ልጆቹ የሚያስፈልጋቸውን የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኙ ያግዛል። በዚህ መንገድ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ስጋትን በመቀነስ የህጻናትን ትምህርት ተሳትፎ እንጨምር እናደርጋለን። ይህም ፕሮጀክት ከአስራ ስድስት ላላነሱ ሰዎች የሥራ እድል የሚሰጥ ሲሆን እንዲሁም ከሁለት በባቱ/ ዝዋይ / ውስጥ ከሚገኙ የወተት ተዋጽኦ አምራችና አቅራቢ ድርጅቶች ጋር የስራ ዉል ተፈራርመናል።

ከአጋሮቻችን ቫን ዲጅክ ፍሎራ እና የኔዘርላንድ ፍላወር ፋውንዴሽን ላደረጉልን ለዚህ ለጋስ እርዳታ በሁሉም የሼር ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች፣ ወላጆች እና አስተማሪዎች ስም እጅጉን የላቀ ምስጋና ልናቀርብላቸዉ እንወዳለን።