Overview News

ሼር ተማሪዎች ተሸለሙ

31 January 2023 Aswin Endeman
Sher students awarded

በቅርቡ ከ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ሶስቱ በተለየ ችሎታ ግኝት እና በፈጠራ ውድድር ላይ ተሳትፈዋል፤ የተለየ ፈጠራ የተዘጋጀዉ በኦሮሚያ ትምህርት ጽ/ቤት ነዉ፡፡ ውድድሩ በክልል ደረጃ የነበረ ሲሆን “በኦሮሚያ ሴት ተማሪዎች ቀን”  ላይ ቀርቧል፡፡ ይህም ዝግጅት በአዲስ አበባ በኦሮሚያ ባህል ማዕከል ተካሄዷል።

በእጅ ጥበብ ዘርፍ ሄለን ዮሴፍ፣ ማህሌት ብርሃኑ እና ቀነኒቱ ተሾመ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ እነሱም ሜዳሊያዎችን እና የምስክር ወረቀት አግኝተዋል፡፡ በእለቱ የጥበብ ስራዎቻቸውን በታዳሚ ፊት እንዲያቀርቡ እድል የተሰጣቸዉ ሲሆን በመምህር ሮቢቲ መንገሻ ታጅበው ነበር፡፡ በዓሉን ለማክበር በማግስቱ የወዳጅነት ፓርክን ለማየት ሄደዋል፡፡

ወደ ሼር ትምህር ቤት ከተመለሱ በኋላም ሴት ልጆች በትምህርት ቤቱ አስተዳደር እና በተማሪዎቻቸው የክብር አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ ሴት ልጆቻችን ጥሩ  ስራ ሰርተዋል፡፡