Category Archives: News

Overview News

አካታች በሆነ መልኩ አለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8/2024 በሼር ኢትዮጵያ ተከበረ

26 March 2024 Mariska Braam

መጋቢት 8 እና 9 አለም አቀፍ የሴቶች ቀን (IWD) በሼር ኢትዮጵያ ተከበረ. Inspire Inclusion የዚህ ዓመት የአለም አቀፍ ጭብጥ  መርህ ነበር፣ እናም በዚህ መሰረት የተለያዩ የውይይት መድረኮች  ተዘጋጅተውም ነበር።

በዕለቱም መጋቢት 8 በድርጅቱ COO አስዊን ኢንዴማን እና በኦፕሬሽን ዳይሬክተሩ አንድሪው ብሩክ ስሚዝ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ፕሮግራሙ የተከፈተ ሲሆን በንግግራቸውም ላይ ሁሉንም ሰራተኞች ላይ በእኩል፣  በንቃት ሲሰራበት እና የሁሉንም ባልደረቦችንን አስተዋፅኦ ስንመለከት ለኩባንያው መሳካት አስፈላጊ መሆኑን አፅንዖት በመስጠት ተናግረዋል።።

ከዚያ በኋላ የሥርዓተ-ፆታ ኮሚቴው በኔዘርላንድ ውስጥ በምትገኝ ዞተርዎዴ ከተማ ምክር ቤት ሴቶች ጋር በበይነ መረብ ስብሰባ በማድረግ በአንድ ላይ የአለም አቀፍ የሴቶች ቀንን እያከበሩ ነበር፣ በዛም ተያይዞ ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እና እርስ በእርስ ለመማማር አበረታች መንገድም አግኝተው ነበር።

መጋቢት 9 ከሁሉም ሰራተኞቻችን ጋር በመሆን በድጋሚ IWD በእርሻችን ላይ አክብረንም ነበር። ይህም በዝዋይ እርሻ ላይ በመግቢያው በር ላይ የፎቶ መነሻ ቦርድ   የተዘጋጀ ሲሆን የስርዓተ-ፆታ ኮሚቴውም ሰራተኞችን በሙዚቃ እና በዳንስ ሲቀበል ነበር በዚህም መርሃ ግብር ውስጥ ብዙ ፎቶግራፎች የተወሰዱ ሲሆን ለብዙዎችም ቀኑ ጥሩ እና አስደሳች የሆነ የስራ ቀንም ነበር።

ወደ ሼር ኢትዮጵያ ለስራ የሚመጣ ሰራተኛ ሁሉ ስለግል ንፅህና ምቾት እንዲሰማው እና አስፈላጊ መሆኑንም አፅንዖት መስጠት ይፈልጋል፣ በዚህ ምክንያት ኩባንያው ‘Mela for her’ መላ ለእርሷ የሚባል እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ እሽጎችን በሁሉም እርሻዎች ላይ ለአበባ ቆራጮች አከፋፍሏል። እንዲሁም በቀጣይ ለሌላ ክፍል ሴት ሰራተኞችም እንዲሁ የሚደርስ ይሆናል።

በመጨረሻም በዝዋይ እርሻ በሚገኘው መዝናኛ አዳራሽ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ኮሚቴው ከሴቶች መብት፣ ከሥርዓተ-ፆታ እኩልነት፣ ከሴቶች በተለያዩ የሕይወት ዘርፎች የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶችና ስኬቶች የሚመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮችን ያካተተ የፓናል ውይይትም ተካሂዷል።

በኩባንያው ውስጥ የሴቶችን ስኬት ያከበርንበት እና አካታች ስራንም ለመስራት ያነሳሳንበትን ታላቅ ቀን መለስ ብለን ስንመለከትም መሪ ቃሉን ‘Invest in women እድገትን ለማፋጠን ይረዳል’ መማለት ሁላችንም ይህንን እንድናስታውስ እና ቀን ከቀን የስራችን አንዱ አካል ልናደርገውም ይገባናል።

Overview News

350 ሴት ልጆች እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ መላ ለእርሷ የተሰኘ የንፅህና መጠበቂያ ፓድዎች ተለግሰዋል

12 January 2024 Aswin Endeman

በ2015 መኸር ላይ የተጀመረውን ፕሮጀክት ተከትሎ፣ በቅርቡ በሼር ትምህርት ቤቶቻችን እድሜያቸው ከ12 እስከ 13 ዓመት የሆናቸው 350 ሴት ልጆች እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ የንፅህና መጠበቂያ ፓድዎችን ሰጥተናል. ይህ ሊሆን የቻለው በኔዘርላንድ የአበባ ፋውንዴሽን ከፍተኛ ድጋፍ ነው።

መላ በአማርኛ መፍትሄ ማለት ሲሆን የሚያመለክተውም በሚያሳዝን ሁኔታ በአፍሪካ ውስጥ ለብዙ ወጣት ሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ ላለው ችግር መፍትሄ ማበጀት ሲሆን ይህም ተመጣጣኝ የሆነ የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች እጥረትን ለማቃለል ያሰበ ሲሆን በአፍሪካ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ያሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ልጃገረዶች ለትምህርት፣ ለጤና፣ በራስ  ካለመተማመን በላይ ለሰብአዊ መብቶች እንቅፋት ይፈጥራል ብሎም ለብዙዎች የወር አበባ መጀመር ማለት በትምህርት ቤት ውስጥ ቀሪ እንዲበዛም ያደርጋል።

መላ እርሷ ሴቶችን እና ልጃገረዶችን በመላው ኢትዮጵያ በተመጣጣኝ ዋጋ እና ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ የወር አበባ ምርቶችን እና የወር አበባን የጤና ትምህርት በመስጠት ህይወትን የሚቀይር የኢትዮጵያ ማህበራዊ ጀማሪ ድርጅት ነው.

በዚህ ፕሮጀክት፣ ሼር-ትምህርት ቤቶች፣ መላ ለእርሷ እና የደች አበባ ፋውንዴሽን ተባብረዋል. የባለሙያዎች ቡድኑ ፓድ ከመስጠቱ በተጨማሪ የሼር ትምህርት ቤት መምህራንን በማሰልጠን በልጃገረዶች ክበብ በኩል ሁሉም ልጃገረዶች በወር አበባ ጤና ላይ ስልጠና ይሰጣቸዋል.

መላ እርሷ ለቡድኑ ፍሬያማ ትብብር ማመስገን እንፈልጋለን እንዲሁም የደች አበባ ፋውንዴሽን ላደረጉት የማይናወጥ ድጋፍ ከልብ እናመሰግናለን. ልጃገረዶች በህይወት ውስጥ ያላቸውን ሙሉ አቅም እንዲደርሱ በማስቻል የክብር መብታቸውን የሚደሰቱበት ዓለም በጋራ እናበረክታለን።

Overview News

የአረጋውያን ቀን አከባበር

2 January 2024 Aswin Endeman

በቅርቡ በባቱ/ዝዋይ ተከበረውን የአረጋውያን ቀንን ስፖንሰር በማድረግ በማህበረሰባችን ውስጥ ያሉ አረጋውያን ያበረከቱትን አስተዋጾ ለማክበር እና ለመዘከር እንዲሁም ለማድነቅ የተዘጋጀ ድንቅ ቀን ነበር። ዝግጅቱ የአረጋውያን   ጠቃሚ ሚና በመገንዘብ ልምዳቸውን ለተተኪው ትውልድ የሚያካፍሉበት መድረክ እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመም ነበር።

ክቡር አቶ አህመዲን እስማኤል (የከተማው ከንቲባ) ካደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በፊትም ከዚህ አለም በሞት የተለዩትን የአረጋውያን በማስታወስ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎትም እንዲደረግ አስተባብረው ነበር።

ሼር ኢትዮጵያም ከ500 ኪሎ ግራም በላይ የበቆሎ ዱቄት እና 50 ሊትር የምግብ ዘይት ለ50 አረጋውያን በስጦታ መልክ  በማስረከብ ለዝግጅቱ ያለውን ተሳተፎም በቀናነት አሳይቷል።

Overview News

በድጋሚ ጌሪት ኤንድ ኔል ባርንሆርን ስኮላርሺፕ ለ 4 ተማሪዎች ተሰጠ

14 December 2023 Aswin Endeman

በቅርቡ ለሶስተኛ ጊዜ የጌሪት ኤንድ ኔል ባርንሆርን ስኮላርሺፕ ለአራት 12ተኛ ክፍልን ላጠናቀቁ የሼር ትምህርት ቤት ተማሪዋች ተሰጥቷል።እንደሚታወቀው የባርንሆርን ቤተሰብ የሼር ኢትዮጵያ እና የትምህርት ቤቶቹ መስራቾች ናቸው.።በየዓመቱ 4 ተማሪዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በመረጡት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሚማሩበት ወቅት አብዛኛውን የጥናት ወጪያቸውን እና ኑሮዋቸውን ለማገዝ ይረዳ ዘንድ በስኮላርሺፕ መልክ በየወሩ ገንዘብ በሼር ኢትዮጵያ በኩል ይላክላቸዋል። የስኮላርሺፑ ዋና አላማ የተቸገሩ ሆነዉ ነገርግን ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን ለመርዳት የሰበ ነው።

ስለዚህም፟ ፣ተማሪ ነኢማ አስቻሌው፣ ጀሚላ ሄዴቶ፣ መሀመድ አህመድ እና ዮርዳኖስ ሻንበል ሽልማታቸውን ከወይዘሮ ሉሊት ታዴለ እና ከ ሚስተር አስዊን ኢንዴማን  አጅ ተቀብለዋል። ሼር ማኔጅመንትን በመወከልም ሚስተር አስዊን ኢንዴማን    አሸናፊዎቹን እንኳን ደስ ያላችሁ  በማለት እና የሼር ትምህርት ቤት መምህራንን እና ደጋፍ ሰጪ ሰራተኞችን ላለፉት 16 አመታት ላደረጉት ትጋት አና ላስመዘገቡት ውጤት አመስግነዋል።

ከሁሉም የ12ተኛ ክፍል ተመራቂዎች ውስጥ 8 ተማሪዎች ተመርጠው 4ቱ ለስኮላሺፕ ሲሰጣቸው ሌሎች 4 ደግሞ ላፕቶፕ ተሸልመዋል ስሥነ ሥርዓቱም የተካሄደው የተማሪ ቤተሰቦች፣ የሸር ኢትዮጵያ ሥራ አስኪያጆች፣ የማኅበረሰብ ሽማግሌዎች፣ የሼር ትምህርት ቤት ሠራተኞች፣ የወላጅ ኮሚቴ እና በርካታ የመንግሥት የከተማዉ አመራሮች በተገኙበት ነው።

አንደሁልጊዜው ሁሉ ጌሪት ባርንሆርን፣ ባለቤታችው ፣ ልጆቻቸው ላለፉት አመታት ለሼር ትምህርት ቤቶች እና ሆስፒታል ላደረጉት የማይናወጥ ድጋፍ አያመሰገንን እነዚህ ተማሪዎች ሼር ኢትዮጵያ ላስመዘገበው አወንታዊ ተፅእኖ እውነተኛ ምሳሌ በመሆናቸው እጅግ ኩራት ይሰማናል ለዝዋይ እና ለአካባቢው ማህበረሰብም ተመልሰዉ አንደሚረዱ አና አንደሚጠቅሙ አምነታችን ነው ሁሉም የ12ተኛ ክፍል ተመራቂ ተማሪዎቻችን በሚሄዱበት ቦታ ሁሉ ብሩህ የወደፊት ህይወት እና መልካም ጊዜ እንመኝላቸዋለን።

በኢትዮጵያ የሚገኙ የሼር ትምህርት ቤቶች ከ6500 በላይ ተማሪዎችን በሶስት ቦታዎች ያስተምራሉ፣ በግምት ወደ 400 የሚጠጉ ልጆች ከ 4ዓመት እድማቸው ጀምሮ በየዓመቱ ወደ ሼር ትምህርት ቤቶች ይገባሉ. ምዝገባዉም የሚከናወነው በ 50% ከሼር ሰራተኛ ልጆች እንዲሁም 50% ደግሞ ከአካባቢው ማህበረሰብ ልጆች በሚደረግ እኩል ክፈፈል ነው።

Overview News

ሼር ኢትዮጵያ አዲስ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአዳሚ ቱሉ ከፈተ

11 December 2023 Aswin Endeman

በህዳር ወር በቀን 11 ሼር ኢትዮጵያ በአዳሚ ቱሉ አዲስ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከፈተ። የመክፈቻ ስነስረዕቱም በፕሮገራሙ ላይ ተጋብዘው በነበሩ እንግዶች የተከበሩ አቶ ኡስማን ቱሴ የባቱ ከተማ ምክትል ከንቲባ ፣ አቶ ከዲር ጀቤሶ የባቱ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ፣ ሚስተር አስዊን ኢንድማን የሼር ኢትዮጵያ የቢዝነስ ድጋፍና ሲኤስአር ስራ አስኪያጅ እንዲሁም አዳሚ ቱሉ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ሽማግሌዎች፣ የሼር ኢትዮጵያ አስተዳደር ተወካዮች፣ መምህራን እና በአጠቃላይ ቁጥራቸዉ 192 የሚደርሱ ተማሪዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከናዉኗል።

ትምህርትን ከክፍያ ነፃ መስጠት የሼር ኢትዮጵያ ዋና እሴት ነው. እ.ኤ.አ. በ 2017 ተጀምሮ የነበረው የሁለተኛው እርሻ ግንባታ በአዳሚ ቱሉ በመጠናቀቁ ድርጅቱ በከተማዉ ውስጥ ባሉ አዳዲስ የትምህርት ቤቶች ላይ ኢንቨስት አያደረገ ይገኛል። በ2019 ሼር መዋዕለህፃናቱን በመክፈት የጀመረው ትምህርት ቤት በአሁኑ ወቅት 342 ተማሪዎችን ይዞ በማስተማር ላይ ይገኛል። ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኋላም የመጀመሪያዎቹ የተማሪዎች ማለትም ቁጥራቸው ከላይ የተጠቀሰው በአሁኑ ወቅት በ አዲሱ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ በመማር ላይ ላይገኛሉ። ሁለቱ ትምህርት ቤቶች በመካከላቸዉ የ500 ሜትር ያህል ርቀት አላቸው።

ሼር በየአመቱ 4 አዳዲስ የመማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት ያቀደ ሲሆን፣ ይህ አዲስ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ8 ዓመታት ውስጥ ወደ 1500 የሚጠጉ ተማሪዎች ያይዛል ግቢውም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ለመጨመር በቂ ነው።

የሸር ትምህርት ቤቶች ከሼር ሰራተኞች ለመጡ ልጆች እና ከአካባቢው ማህበረሰብ ለመጡ ልጆች አቅም በፈቀደ ሁሉ ክፍት ናቸው።

ይህንን አዲስ ትምህርት ቤት እውን ለማድረግ ለረዱ ሁሉ ምስጋናችን ከልብ ነው። ከራሳችን የግንባታ ቡድን እስከ ሲቪል ሰርቫንቶች፣ ከመምህራን እስከ ጽዳት ሠራተኞች ድረስ ለሁሉም ምስጋናችን ይድረሳቸው።

ይህ ትምህርት ቤት ለአዳሚ ቱሉ ማህበረሰብ የአንድነት፣ የእድገት እና የዘላቂ መንፈስ ምልክት ይሁን እያልን ብዙዎች የሚማሩበት እና የእውቀት ነበልባል ከአንድ ትውልድ ወደ ሌላው ትውልድ የሚተላለፍበት ቦታ ይሁን ዘንድ ምኞታችን ነው።

Overview News

አዲሱ አመት ያቀዱት የሚሳካበት ፣ ውጥኖ የሚሰምርበት፣ በጤና በሰላም በደስታ የሚዘልቁበት መልካም አዲስ አመት ይሁን።

12 September 2023 Aswin Endeman

Overview News

የአካል ጉዳት ላለባቸው ሠራተኞቻችን የተደረገ ድጋፍ

11 September 2023 Aswin Endeman

ባለፈው ሳምንት በፌርትሬድ  መርሃግብር ስር ባለው DONUTS program ፕሮግራም  በኩል የተለያዩ የአካል ድጋፍ መስጫ መሳሪያዎችን ማግኘት የቻልን ሲሆን ከነዚህም ውስጥ  መነጽር ፣ ክራንቾች፣ ምቹ ጫማዎች ፣ሰው ሰራሽ እግሮች  ቁጥራቸው ከፍ ላለ ሰራተኞቻችን ማሰራጨት ችለናል።

ይህም ለ 4 ዓመታት የሚዘልቅ መርሃ ግብር ሲሆን ዓላማዎቹም  የሥርዓተ ጾታ እኩልነት ፣ ወጣቶች እና ተጋላጭ የሆኑ ቡድኖችን እና በተለይም የአካል ጉዳተኞችን ማበርታት እና መደገፍ ናቸው።  ከዚህ በተጨማሪ መርሃግብሩ የፌርትሬድ ምርት  አምራች ድርጅቶችን አቅም  እና የሠራተኛ ማህበራትንም አቅም ለማጎልበት ዓላማ ያለው ፕሮግራም ሲሆን  በፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል የገንዘብ ድጋፍም ተደርጎለታል።

ሼር ኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ  ሠራተኞችን ማካተት ሁል ጊዜ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው፣ ስለዚህም የ DONUTS ፕሮግራም ለ108   የአካል ጉዳተኛ ሠራተኞቻችን በመሳሪያ በመደገፉ ከፍ ያለ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።

በዚህ ፕሮጀክት ሼር ኢትዮጵያ እና ፌርትሬድ አፍሪካ ከ ግራር ቤት ተሃድሶ  ማህበር ጋር ተባብረዋል  ማህበሩም የተጠየቀውን የመሣሪያ አይነት እና መሳሪያዎቹም በትክክለኛ  ሁኔታ መገጣጠም እንዲችሉ  ለመወሰን ይረዳ ዘንድ ለተጠቃሚዎች ልኬቶችን በቅድሚያ አከናውኗል በዚህም መሰረት ቀደም ተብሎ የተጠቀሱት ክራንቾች  ፣ ሰው ሰራሽ እግሮች ፣  ምቹ ጫማዎች መነጽር እና መስማት የሚያስቸሉ መሣሪያዎችን ለ108 ሠራተኞቻችን ማዳረስ በመቻላችን እናም እነሱም በምቹ ሁኔታ መኖር እና  መሥራት መቻላቸውን በማየታችን ደስተኞች ነን። ለተከበሩ አጋሮቻችንም የላቀ ምስጋናችንን  በድጋሚ እናቀርባለን።

 

Overview News

የዓለም ጽዳት ቀን

29 August 2023 Aswin Endeman

እ.ኤ.አ. መስከረም 5 በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች አከባቢያቸውን ከቆሻሻ ለማፅዳት ኃይላቸውን አጠናክረው የሚቀሳቀሱበት የጽዳት ቀን ነው። በሼር ኢትዮጵያም በተለምዶ በየሦስት ወሩ ይህ የጽዳት ዘመቻ የሚከናወን ሲሆን በአዲሚ ቱሉ እና በቆቃ እርሻዎቻችንን ላይም እንዲሁ አከባቢን ለማፅዳት በንቃት እንሳተፍለን።

በባቱ /ዝዋይ በሚገኘው እርሻችን ደግሞ ከጎረቤት እርሻዎች ጋር በመቀናጀት እና ሃይልን በማስተባበር በጥቅሉ ከ 100 በላይ የሼር  ኢትዮጵያ ሠራተኞች በየ ሶስት ወሩ በእነዚህ የጽዳት ዘመቻዎች ላይ ይሳተፋሉ።

ጥቃቅን ቆሻሻን ማየት ደስ የማያሰኝ ብቻ ሳይሆን አካባቢውን ይበክልና ወደ ወንዞች ፣ ሐይቆች እና ውቅያኖሶች ይጎዛል በመጨረሻም ስነ ምህዳሩንም ፣ፕላኔቷንም አደጋ ላይ ይጥልና ጤናችንን የሚጎዳ ይሆናል።

በዓመት አንድ ጊዜ ማፅዳት ብቻ ሳይሆን በየሩብ ዓመቱ ሁሉ በትጋት የሚሰሩ ሰራተኞቻችንን እና በጎ ፈቃደኞቻችን ማመስገን እንወዳለን በዚህም መሰረት በመስከረም 5 የዓለም የጽዳት ቀንን ስለምናከብር ሁሉም ሰው ኃይሉን ሰብስቦ እንዲቀላቀለን ጥሪያችንን እናቀርባለን።

 

Overview News

የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ

9 August 2023 Aswin Endeman

የአየር ንብረት ለውጥን እና የደን ጭፍጨፋን ለመግታት ያቀደው አረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ቀድም ሲል በሀገሪቱ ከ6 ዕመታት በፊት የተጀመረ ሲሆን እስካሁን ድረስ በመላው ኢትዮጵያ 3.7 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንደተተከሉ ይነገራል።. በዚህም መሰረት በየዓመቱ ለዘመቻው አስተዋፅኦ  የምናደርግ ሲሆን በዚህም ዕመት በሐምሌ ወር የሥራ ባልደረቦቻችን በወርጃ እና በቃሞ ገርቢ ጋራዎች ላይ ከ 46.000 በላይ ችግኞችን በመትከል ተሳትፈዋል፣ ይህንንም በአከባቢው የአስተዳደር ጽ/ቤት ፣ በአከባቢው ባለሀብቶች እና በማህበረሰቡ ትልቅ ትብብር ማሳካት ተችሏል።

በተጠበቁ አካባቢዎች ችግኞችን ከመትከል በተጨማሪ በ 4ቱ የሼር ት/ቤቶችም ጊቢ ውስጥ 300 የፍራፍሬ ተሸካሚ ዛፎችን እና 1.000 ሌሎች ችግኞችን ተክለናል። በጥቅሉ በዘመቻው የተሳተፉትን የሥራ ባልደረቦቻችን እና በጎ ፈቃደኞችን ሁሉ ለማመስገን እንወዳለን።

 

Overview News

አፍሪፍሎራ፣ ደች ፍላወር ግሩፕ እና ካማራ ኤዱኬሽን በሼር ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ሁለት የIT ክፍሎችን በጋራ አዘምነዋል።

3 July 2023 Aswin Endeman

በደች ፍላወር ፋውንዴሽን እና በአፍሪፍሎራ ለጋስነት በዝዋይ በሚገኘው ሼር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ ሁለት አዲስ የኢ-መማሪያ ማዕከላትን ማቋቋም ችለናል።

ካማራ ኤዱኬሽን 50 አዳዲስ ኮምፒውተሮችን እና ሁለት ሰርቨሮችን የተከለ ሲሆን ፣ ኮምፒውተሮችን ለት/ቤት የሚያቀርብ እንዲሁም መምህራንን እያሠለጠነ፣  በገጠር እና ሩቅ በሆኑ የኢትዮጵያ ክፍሎች  ለትምህርት ምቹ የሆኑ የኮምፒዩተር ክፍሎችን በማቋቋምና አስተማማኝ እንዲሁም ከወረቀት እና ከአቧራ-ነጻ አካባቢን በመፍጠር ያግዛል።

አሰልጣኞችም ለአንድ ሳምንት ያህል በሼር ኢትዮጵያ ትምህርት ቤት ተገኝተው 26 መምህራንን የኮምፒዩተር አጠቃቀም በስርአተ ትምህርቱ መሰረት በማሰልጠን እና በመሰረታዊ ጥገና ላይ ምክር ሰጥተዋል።

የካማራ  ኮምፒውተሮች በኡቡንቱ ክፍት ምንጭ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ላይ ይሰራሉ። ከቀላል  እስከ ልዩ የካማራ መማሪያ ስቱዲዮ ግብአቶችን ለሂሳብ እና ለሳይንስ የተለያዩ ትምህርታዊ ሶፍትዌሮች ተጭነዋል። ብሎም ኮምፒውተሮቹ እንዲሁ ከመስመር ውጭ የሆነው ዊኪፔዲያም ተጭኖላቸዋል፣ ይህም ውስን የበይነመረብ ግንኙነት ላላቸው ትምህርት ቤቶች ያልተለመደ የመማሪያ ምንጭ ይፈጥራል። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኮምፒውተሮቹ በፒዲኤፍ የተጫኑ የትምህርት ሚኒስቴር የመማሪያ መጽሃፍቶች አጠቃላይ የትምህርት ቤቱን ሥርዓተ ትምህርት ያካተቱ ናቸው። በብዙዎቹ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች 40,000 ለሚጠጉ የመማሪያ መጽሀፍት አቅርቦት በጣም ውስን በመሆኑ ይህ ብቻውን ጥሩ ግብአት ይሆናል።

የደች ፍላወር ፋውንዴሽን  የተቸገሩ ሰዎችን እና በተለይም የህጻናትን የኑሮ ሁኔታ እና ደህንነት ለማሻሻል ያለመ ነው።   የደች ፍላወር ቡድን (DFG) አጋሮቹ በተገኙበት ቦታ የማህበረሰብ ፕሮጀክቶች ላይ በማተኮር የሚሰራ ነው። ቡድኑም /DFG ለምንኖርበት አለም ያለውን ሀላፊነት እየተወጣ ይገኛል።

በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችም በዚህ ተጠቃሚ ይሆናሉ ይላሉ የሼር ትምህርት ቤት ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ አጋ፡ የኮምፒውተር ችሎታ ለተማሪዎቻችን እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው። ሼር-ትምህርት ቤት  በኢትዮጵያ ጥሩ ስም ካላቸው ት/ቤቶች ውስጥ አንዱ ነው። ሁሉም ተማሪዎች ማለት ይቻላል ዩኒቨርሲቲ ለመግባት ብቁ ይሆናሉ። አዳዲሶቹ የኮምፒውተር ክፍሎቸም ስማችንን ብሎም ደረጃችንን እንድናስጠብቅ እና ዲጂታል አለምን ለተማሪዎቻችን እንድንከፍት ያስችሉናል።

አፍሪፍሎራ በኢትዮጵያ ውስጥ ሼር ኢትዮጵያ በሚል ስም ሶስት እርሻዎች አለው። በሼር ትምህርት ቤቶች 6800 ልጆች ከመዋዕለ ሕፃናት እስከ ሁለተኛ ደረጃ ድረስ ትምህርት  በነፃ  ያገኛሉ።

ደች ፍላወር ግሩፕ እና ካማራ  በዚህ ፕሮጀክት ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላቅ ያለ አድናቆት  ያለን ሲሆን በተማሪዎቹ እና በመምህራን ስም ከልብ ለመምስገን እንወዳለን።